“እግዚአብሔር በአንድም መንገድ በሌላም ይናገራል።” ኢዮ.33፥14

ወቅታዊ ትምህርት

ተጨማሪ ይመልከቱ

ባሕረ ሐሳብ የዘመን መቁጠሪያ

ይህ ሶፍትዌር ከዚህ በፊት 2000 .. /..አ. በ2008 / በተለቀቀው ሶፍትዌር ላይ አንዳንድ ማስተካከያዎች በማድረግ ማተም /ፕሪንት ማድረግ/ ንዲቻል ተዘጋጅቶ የቀረበ ነው። ወደ ኮምፒዩተርዎ በመጫን ይጠቅሙ።

BahireHasabSetupIcon.JPG ሶፍትዌሩን እዚህ በመጫን ይጠቅሙ።

ቀዳሚ ገጽ
የነነዌ ሰዎች የንስሐ ምስክሮች
በዲ/ን በረከት አዝመራው

የነነዌ ጾም ከሰባቱ የቤተክርስቲያን አጽዋማት አንዱና የዐቢይ ጾም ማዘጋጃ ደወል ነው፡፡ ይህ የነነዌ ሰዎች የንስሐ ታሪክ በቤተክርስቲያናችን በጣም ታላቅ ዋጋ ያለውና የራሱ መዝሙር የሚዘመርለት፣ ቅዳሴ የሚቀደስበት ታላቅ መታሰቢያ ያለው ታሪክ ነው፡፡ ራሱ ጌታችንም የነዌ ሰዎችን የንስሐ ታሪክ በመጥቀስ አይሁድን ገስጾበታል፤ በፍርድ ቀንም በዚያ ትውልድ ዘንድ እንደሚፈርዱበት ተናግሯል፡፡ ይህም የሆነበት የነነዌ ሰዎች ደስ የሚያሰኝ የንስሐ ታሪክ ስላላቸው ነው፡፡ በዚህ ጽሑፍ ይህን አስደሳች የንስሐ ታሪክ በጾመ ነነዌ ከሚነበቡ የቅዳሴ ምንባባት አንጻር ለመመርመር እንሞከራለን፡፡
ኃጢአት ከእግዚአብሔር መለየት እንደሆነ ሁሉ ንስሐ ደግሞ ወደ እግዚአብሔር መመለስ ነው፡፡  በዚህ ከእግዚአብሔር ሊለዩ የሚችሉ ብዙ ፈተናዎች ባለቡት ዓለም እስካለን ድረስ ሕይወታችን ሁሉ የንስሐ ጊዜ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ከሁሉም ጊዜ በተለየ ወደ እግዚአብሔር የምንመለስባቸው የጾም ወቅቶች ሲሆኑ ከእነዚህም ታላቁና ዋነኛው ዐቢይ ጾም ነው፡፡
Share
ዝርዝር ንባብ...
 
ጾመ ነነዌ!!

ጥር 25/2004 ዓ.ም.

በገብረእግዚአብሔር ኪደ

ነነዌ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ታሪካቸው በስፋት ከተጻፈላቸው የሜሶፖታምያ ከተሞች አንዷ ናት፡፡ ብዙ የሥነ መለኲት ምሁራን ከዛሬዋ የሞሱል ከተማ በተቃራኒ ከባግዳድ ሰሜን ምዕራብ 350 ኪ.ሜ. ርቀት ላይ እንደ ነበረች ይስማማሉ፡፡ ምንም እንኳን በ4000 ቅ.ል.ክ. ገደማ በናምሩድ በኩል ብትቆረቆርም /ዘፍ.10፡11-12/ የአሦራውያን ዋና ከተማ የሆነችው ግን በ1400 ቅ.ል.ክ. ነው /2ነገ.19፡36/፡፡ በከተማዋ በጣም ታዋቂ የነበረው የጣዖት ቤተ መቅደስ የአስታሮት ቤተ መቅደስ ይባላል፡፡
Share
ዝርዝር ንባብ...
 
የቅዱሳት መጻሕፍት ንባብ
ጥር 22/2004 ዓ.ም
በዲ/ን አሻግሬ አምጤ


ቅዱሳት መጻሕፍት ከሥጋዊ አስተሳሰብ የተለዩ ለትምህርት፣ ለተግሳጽ ልብንም ለማቅናት፣ በጽድቅም ላለው ምክር የሚጠቅሙ ናቸው፡፡ /1ጢሞ.3፥16/ ያላወቁትን ለማወቅ፣ የበደሉትን ይቅር በለኝ ለማለት፣ ጠማማውን ልብ ለማቅናት፣ በእውነት መንገድ ለመጓዝ የሚያገለግሉ ቅዱሳት መጻሕፍት አሥራው ወይም ቀኖናውያንና አዋልድ ተብለው በሁለት ይከፈላሉ፡፡


orthodoxmonkአሥራው መጻሕፍት ሕግጋት፣ መመሪያ፣ የእግዚአብሔር ዓላማና እቅድ ጠቅለል ተደርጎ የቀረበባቸው ሲሆኑ አዋልድ መጻሕፍት ደግሞ “ከመጽሐፍ ቅዱስ ሐሳብና እውነታ ሳይወጡ ኀይለ ቃሉንና ውስጠ ምስጢሩን የሚተረጉሙ፣ የሚያብራሩ፣ የሚተነትኑ ናቸው፡፡” /ዳንኤል 1999፥64/ እምቅ፣ ጥቅልና ምስጢራዊ የሆነው መጽሐፍ ቅዱስ በትርጓሜ መጻሕፍት፣ በጸሎት መጻሕፍት፣ በገድላት፣ በድርሳናትና መሰል ጽሑፎች ተብራርተው፣ ተተንትነው ሲቀርቡ የይዘት ለውጥ ባይኖርም በባህል፣ በእድገት ደረጃ በመልክአ ምድራዊ አቀማመጥ፣ በኑሮ ዘይቤ አንፃር ሊለያዩ ይችላሉ፡፡ የሚያመጣው ልዩነት የይዘት፣ የአስተምህሮ፣ የነገረ ሃይማኖት እንዳይሆን ንባብንም ሆነ ትርጓሜን እንደ ሥጋ ፈቃድ ከመሔድ መቆጠብ ይገባል፡፡ ቅዱሳት መጻሕፍት ቅዱሳን ሰዎች በመንፈስ ቅዱስ ተመርተው እንደጻፉት የሚተረጉሙትም በመንፈስ የሚመሩ መሆን ይገባቸዋልና፡፡

Share
ዝርዝር ንባብ...
 
የግቢ ጉባኤያት ተማሪዎች የንስሐ አባቶች ሴሚናር ተካሔደ
በ ዲ/ን  ኅሩይ ባየ

kahinatSeltenaበማኅበረ ቅዱሳን አዘጋጅነት ከጥር 16-18 ቀን 2004 ዓ.ም ድረስ  የግቢ ጉባኤያት ተማሪዎች የንስሐ አባቶች ሴሚናር   በማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል  ተካሔደ ፡፡

 

በማኅበረ ቅዱሳን የሀገር ውስጥ ማዕከላት ግቢ ጉባኤያት ማደራጃና ማስተባበሪያ ዋና ክፍል ሓላፊ የሆኑት ዲያቆን አንዱአምላክ ይበልጣል እንደገለጡት የንስሐ አባቶች በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚገኙ ተማሪዎችን ዘመኑን የዋጀ ትምህርት እንዲያስተምሩና አባታዊ ተልእኳቸውን እንዲወጡ ሴሚናሩ እንደሚያግዛቸው አብራርተዋል፡፡ በተጨማሪም በሥልጠናው ላይ የተገኙ ካህናት ከተለያዩ ቦታ የመጡ በመሆናቸው በአንድ የሥልጠና ቦታ ተገኝተው ልምዳቸውን እንዲለዋወጡና እንዲመካከሩ ለማድረግ ታስቦ የተዘጋጀ ሴሚናር መሆኑን ገልጠዋል፡፡

Share
ዝርዝር ንባብ...
 
ዘመነ መርዓዊ /የሙሽራ ዘመን/
በመ/ር ኃይለማርያም ላቀው

HolyMarriageየጋብቻ ሕይወት በኤደን ገነት እንደተጀመረ ይታወቃል፡፡ ዘፍ 2÷26 በዘመነ ሐዲስም መርዓዊ ሰማያዊ ክርስቶስ በቃና ዘገሊላ ከእመቤታችን ጋር ተገኝቶ የዶኪማስን ጋብቻ ባርኳል ፣ ቀድሷል፡፡ ዮሐ 2÷1-10፡፡ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቃና ዘገሊላ ጋብቻን መባረኩን፣ ዓለምን ለማስተማር መገለጡን ለማዘከር ከጥር መባቻ እስከ ዐቢይ ጾም መግቢያ ያለውን ወቅት ‹‹ዘመነ መርዓዊ›› በማለት ትጠራዋለች፡፡ በመሆኑም በዚህ ወቅት በኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ጸንተው ፣በድንግልና ራሳቸውን ጠብቀው ለኖሩ ሥርዓተ ተክሊልን በመፈጸም አንድ ታደርጋቸዋለች፡፡
Share
ዝርዝር ንባብ...
 
<< ጀምር < ወደኋላ 1 2 3 4 5 6 7 ወደፊት > መጨረሻ >>

ገጽ 1 ከ 7

ግጻዌ

Difficulty with characters ?

Click here! if you have difficulty reading amharic(geez) characters

ማስታወቂያ

multimedia site

 

 

የጽሑፎች ማውጫ - በወራት