የእለቱ ጥቅስ

እስከ ሞት ድረስ የታመንህ ሁን - ራዕ. 2.10

Site Last Updated:-Wednesday 10 March 2010
ቅድመ ገጽ
ደብረ ዘይት

ብዙዎች በስሜ ይመጣሉ /ማቴ.24.1-36/
በአባ ዘሚካኤል

 የዐቢይ ጾም አምስተኛው ሳምንት ደብረ ዘይት ይባላል፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርሰቶስ በደብረዘይት ነገረ ምጽአቱን እንዳስተማረ የሚነገርበት ሳምንት ነው፡፡ «ወእንዘ ይነብር እግዚእነ ውሰተ ደብረዘይት ቀርቡ ኀቤሁ አርዳኢሁ እንተበህቲቶም» ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደብረ ዘይት ተቀምጦ ሳለ ስምዖን፣ ጴጥሮስ፣ ያዕቆብና ዮሐንስ እንድርያስን ጨምሮ ቀርበው «ንገረን ይሄ መቼ ይሆናል?» በማለት ጥያቄ ጠየቁት፡፡ ጥያቄውም የዓለም መጨረሻውና የመምጫህ ምልክቱ ምንድን ነው? የሚል ነበር፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ...
 
ከጋምቤላ ክልል የመጡ ሠልጣኞች ተመረቁ

በማኅበረ ቅዱሳን የትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ክፍል አስተባባሪነት ከጋምቤላ ክልል የአኝዋክና የኑዌር ብሔረሰብ ተወላጅ ሠልጣኞች ተመረቁ፡፡ በማኅበረ ቅዱሳን የትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ዋና ክፍል ሓላፊ ዲ/ን አንዱአምላክ ይበልጣል እንደተናገሩት በክልሉ ከ1997 ዓ.ም ወዲህ ሠልጣኞች መጥተው ሲሠለጥኑ የአሁኑ የመጀመሪያ ጊዜ ነው፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ...
 
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪክና እምነት አጭር ዳሰሳ
«ኢትዮጵያ» የሚለው ቃል «የተቃጠለ ፊት» የሚል ትርጉም ያለው የግሪክ ጥምር ቃል ነው፡፡ ቃሉን ከግብጽ በስተ ደቡብ እስከ ህንድ ውቅያኖስ ድረስ ያለውን ቦታ ለማመልከት ለመጀመሪያ ጊዜ የተጠቀሙበት ሆሜርና ሄሮዱተስ የተባሉት ግሪካውያን የታሪክ ጸሐፊዎች ናቸው፡፡
. . .
«ኦርቶዶክስ» የሚለው ቃል ቀጥተኛ /ትክክለኛ/ የሚል ትርጉም ያለው የግሪክ ጥምር ቃል ነው፡፡ይህንን ቃል ለመጀመሪያ ጊዜ ለቤተ ክርስቲያን ቅጽልነት /ገላጭነት/ የተጠቀሙት በ325 ዓ.ም በኒቅያ /የዛሬይቱ ኢስታንቡል አጠገብ የምትገኝ ከተማ/ የተሰበሰቡት ጳጳሳትና የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት ናቸው፡፡
. . .
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ምንጮች ሦስት ናቸው፡፡ እነዚህም፡-

. . .

ግጻዌ
Difficulty with characters ?
Click here! if you have difficulty reading amharic(geez) characters
ምን ተለወጠ ?